Saint Basilios Theological College Logo
ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ

ጽሑፍ እና ዜና

Theological journals, news updates, and research papers

Debre Berhan Saint Basilios Theological College to Launch Weekend Extension Program in Shewarobit for the 2019 E.C. Academic Year
ዜና 7/22/2026

የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በሸዋሮቢት ከተማ ትምህርት ሊጀምር መሆኑን አበሠረ።

ሐምሌ ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (አቡቀለምሲስ ሚዲያ ፤ ደብረ ብርሃን) የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሸዋሮቢት ከተማ ቅዳሜ እና እሁድ በኤክስቴንሽን ትምህርት ለማስተማር መዘጋጀቱን አብሥሯል። ይህ የምሥራች ይፋ የተደረገው የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች ከሸዋሮቢትና ከቀወት ወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ ሓላፊዎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ባካሔዱት ውይይት መሆኑ ተገልጿል። በዕለቱ በስፋት ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ አመራሮች፡-ዶክተር አቤሴሎም ነቅዐጥበብ፦የቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ዋና ዲን፣ ሊቀ አእላፍ ዮርዳኖስ አቢ፦ የቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምክትል ዲን፣ ሊቀ ልሳናት ደበበ ፍልቄ፦የቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ አካዳሚክ ዲን ናቸው። አመራሮቹ በገለጻቸው ኮሌጁ የሚያስተምራቸውን የትምህርት መስኮች እና የትምህርት አሰጣጥ ሂደቶችን አብራርተዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎች ለአካባቢው ቅድሚያ በመስጠት ለተደረገላቸው መልካም እድል ለሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስን የላቀ ምስጋና አቅርበዋል። በተመሳሳይ ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ አመራሮች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፣ ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን ስኬትም የድርሻቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል። በውይይቱ ላይ የሸዋሮቢት ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት፣ የቀወት ወረዳ ቤተ ክህነት እንዲሁም የአጎራባች ወረዳዎች ካህናት፣ ዲያቆናት፣ መዘምራን እና የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ተሳትፈዋል ሲል የዘገበው ሸዋሮቢት ከተማ ቤተ ክህነቱ ሚዲያ ነው።

Debre Birhan Saint Basilios Theological College Reviews Its Five-Year Strategic Plan
ዜና 7/6/2026

ኮሌጁ የአምስት ዓመት ስትራቴጅካዊ ዕቅድ ክለሳ አደረገ።

የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የነበረውን የ5 ዓመት ስትራቴጅካዊ ዕቅድ ይዘትና አፈጻጸም ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመ የዕቅድ ክለሳ አድርጓል። የኮሌጁን የትምህርት ጥራት፣ የምርምር አቅምና የማኅበረሰብ አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ ለማዘመን ታስቦ የተመደበው ይኸው የምሁራን የባለሙያዎች ቡድን (Team) የመጀመሪያውን ረቂቅ ሰነድ ግምገማ በኮሌጁ የቦርድ ጽሕፈት ቤት አካሒዷል። ይህ የስትራቴጅካዊ ዕቅድ ክለሳ ኮሚቴ የተዋቀረውና ሥራውን የጀመረው በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታዊ መመሪያ ሰጪነትና የበላይ ጠባቂ መሆኑ ተመልክቷል። ክለሳው ተቋሙ በአገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የነባር መንፈሳዊና ዘመናዊ ዕውቀት ማዕከልነት ሚና ለማጠናከርና የዘመኑን ተለዋዋጭ ፍላጎቶች ለመዋጀት ትልቅ መሠረት እንደሚጥል ይጠበቃል። የተሰየመው የምሁራን ቡድን በስትራቴጅካዊ ዕቅዱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት፣ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበትና አዳዲስ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ አሠራሮችን በማካተት ተቋማዊ ራእዩን ዳር የሚያደርስ የተሟላ ሰነድ በቅርቡ አጠናቆ ለቦርዱ እንደሚያቀርብም ተመላክቷል።

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መሠረትን እናጽና!