Saint Basilios Theological College Logo
ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ

የሀላፊዎች መልዕክት

የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በመ/ፓ/ጠ/ጽ/ት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የኮሌጁ በላይ ኃላፊ መልእክት

እንኳን ወደ ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በደህና መጡ! በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ በመጀመሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ስም የተሰየመው የዚህ ኮሌጅ ኃላፊ ሆኖ ማገልገል ክብርም መታደልም ነው። የኮሌጁን ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት ዘወትር በመምራት እንተጋለን። ኮሌጁ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮት ጥልቅ ዕውቀትን ለማዳረስና የምእመናንን ሕይወት በእምነት፣ በዕውቀት፣ በመንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለመቅረጽ ከተቋቋሙት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል አንዱ ነው።


የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎቻችን የዘመናዊውን ዓለም ውስብስብነት ለመከታተል የሚረዱ መንፈሳዊና ዘመናዊ ዕውቀትን ገንዘብ ያደረገ ጊዜ የማይሽረው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና አስተምህሮን ለመስጠት ዛሬም እንደ ትላንቱ በትጋት ለመሥራት ተዘጋጅተናል፡፡ ኮሌጁ በነገረ መለኮት፣ በሕግ፣ በቱሪዝምና ቅርስ አስተዳደር የትምህርት ዘርፎች ላይ የአካዳሚክ የልሕቀት ማእከል ለማድርግ ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያናችንን ልጆች በእምነት፣ በሥነ ምግባርና በመንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ሕይወት የሚበለጽጉበት መካነ አእምሮ እንዲሆን ጭምር ነው። በኮሌጁ የሚሰጠው ሁለገብ ትምህርት መንፈሳዊ ጉዞን የሚያሳካ የጥበብ፣ የሃይማኖትና የሥነ ምግባር ዕውቀት አድማስን ለማስፋት የሚጠቅም ነው፡፡


የኮሌጁ መምህራንና ሠራተኞቻችን እያንዳንዱን የመማር ማስተማር ሂደት ለመደገፍ ለማጠንከር ቁርጠኛ ናቸው። በአንድነት በትምህርት የላቀ ደረጃን እየተቀበልን የእምነታችንን እሴቶች ለመጠበቅ እንጥራለን። በኮሌጃችን ትምህርት ጉዞ ውስጥ በምትገቡበት ጊዜ የሚጠብቃችሁን የመማር፣ የመመራመርና የአገልግሎት እድሎች እንድትጠቀሙ እናበረታታችኋለን። የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን አስተምህሮዋን በማስከበር የቆየ ትውፊቷን ትጠብቁ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው፡፡ በቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ቆይታችሁ እምነታችሁን በማጠናከር፣ ግንዛቤያችሁን በማስፋት፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለኅብረተሰቡ ትርጉም ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አስተዋጽኦ እንደምታደርጉ የፀና እምነት አለን። በመጨረሻም የኮሌጁ ማኅበረሰብ አካል ለመሆን ስለመረጣችሁ እናመሰግናለን።


ወስብሐት ለእግዚአብሔር


አባ ቀሌምንጦስ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በመ/ፓ/ጠ/ጽ/ት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ



Message from Dean of St. Basilios Theological College

Welcome to St. Basilios Theological College!


As the Dean, it is my honor and privilege to welcome you to this esteemed institution, dedicated to the pursuit of theological knowledge, spiritual growth, and the formation of future leaders in faith and service.


St. Basilios Theological College is proud to offer three distinguished faculties: Theology, Law, and Tourism and Heritage Management. Each faculty is designed to provide a rigorous academic environment rooted in the rich traditions of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church (EOTC), while also engaging with contemporary challenges and opportunities in these fields.


At St. Basilios, we are committed to equipping students with the tools necessary for thoughtful reflection, compassionate ministry, and faithful witness in the world. Our mission is to foster intellectual inquiry, spiritual discipline, and communal support, ensuring that every student is prepared to make a meaningful impact in their chosen vocation.


Whether you are here to deepen your understanding of Orthodox teaching and theology, prepare for ordained ministry, explore the intersections of faith and culture, or pursue studies in law or heritage management, you are now part of a vibrant and supportive community. Our faculty, staff, and fellow students are here to walk alongside you on this transformative journey.


May your time at St. Basilios be enriching, inspiring, and transformative. Let us work together to grow in wisdom, faith, and love as we serve God and our neighbors.


I encourage you to explore our website, review our degree offerings, and learn more about who we are. If you have any questions, please feel free to contact me directly.


In Christ’s service,


Abeselom Nekatibeb, PhD

Assistant Professor of Philology, Dean, St. Basilios Theological College

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መሠረትን እናጽና!