የደብረ ብርሃን ቅዱስ ባስልዮስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የነበረውን የ5 ዓመት ስትራቴጅካዊ ዕቅድ ይዘትና አፈጻጸም ወደ ላቀ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመ የዕቅድ ክለሳ አድርጓል። የኮሌጁን የትምህርት ጥራት፣ የምርምር አቅምና የማኅበረሰብ አገልግሎት ተደራሽነት ይበልጥ ለማዘመን ታስቦ የተመደበው ይኸው የምሁራን የባለሙያዎች ቡድን (Team) የመጀመሪያውን ረቂቅ ሰነድ ግምገማ በኮሌጁ የቦርድ ጽሕፈት ቤት አካሒዷል። ይህ የስትራቴጅካዊ ዕቅድ ክለሳ ኮሚቴ የተዋቀረውና ሥራውን የጀመረው በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ አባታዊ መመሪያ ሰጪነትና የበላይ ጠባቂ መሆኑ ተመልክቷል። ክለሳው ተቋሙ በአገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን የነባር መንፈሳዊና ዘመናዊ ዕውቀት ማዕከልነት ሚና ለማጠናከርና የዘመኑን ተለዋዋጭ ፍላጎቶች ለመዋጀት ትልቅ መሠረት እንደሚጥል ይጠበቃል። የተሰየመው የምሁራን ቡድን በስትራቴጅካዊ ዕቅዱ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት፣ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበትና አዳዲስ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ አሠራሮችን በማካተት ተቋማዊ ራእዩን ዳር የሚያደርስ የተሟላ ሰነድ በቅርቡ አጠናቆ ለቦርዱ እንደሚያቀርብም ተመላክቷል።
አስተያየቶች (1)
በጣም ጥሩ ነው።
Submit a Comment